የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን

የስልታዊ ቡድን ምክክር ዛሬም ቀጥሎ ውሏል

የስልታዊ ቡድን ምክክር ዛሬም ቀጥሎ ውሏል

ሐምሌ 23/2018 ዓ.ም

በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው 250 አባላት ባሉት 16 ስልታዊ ቡድኖች የተደራጁ ተመካካሪዎች ምክክር ዛሬ ሐምሌ 23/2018 ዓ.ም ቀጥሎ ውሏል፡፡

በ250 አባላት የተደራጁ 16 ስልታዊ ቡድኖች ከጥቃቅንና ንዑስ ቡድኖች በተገኙና በተጠናቀሩ የአጀንዳ ምክረሃሳቦች ላይ ከትላንት ሐምሌ 22/2018 ኣ.ም ጀምረው ተመካክረዋል፡፡

ትላንት ሐምሌ 22/2018 ዓ.ም በነበረው የምክክር ውሎ ከእያንዳንዱ ሰልታዊ ቡድን በተመረጡ 25 የአጀንዳ ምክረሃሳብ አጠናካሪዎች አማካኝነነት የተጠናቀሩ ምክረሃሳቦችን ያዳመጠው 16ቱ ባለ 250 አባላት ስልታዊ ቡድን፣ በጥቃቅንና በንዑስ ቡድኖች ተነስተው በቀረበው ቃለ ጉባኤ ላይ ያልተካተቱ፣ በአግባቡ ያልተብራሩ ያላቸውን ሃሳቦች ማቅረቡ አይዘነጋም፡፡

ስልታዊ ቡድኖቹ በዛሬው ውሏቸው የተሰጡ አስተያየቶች ተካተውበት በድጋሜ የተደራጀውን ቃለ ጉባኤ የጋራ በማድረግ በቀጣይ ለሚደረገው እና 500 ተመካካሪዎችን ለያዙ 8 ቡድኖች ምክክር ዝግጅት ሲያደርጉ ውለዋል፡፡

በነገው ዕለት በሀገራዊ ምክክር ጉባኤው የውሳኔ አሰጣጥ ሂደት ላይ እገዛ የሚያደርጉ የክልል (ከተማ መስተዳደር) እና የፌዴራል ተወካዮች ምርጫ የሚደረግ ይሆናል፡፡

ኢትዮጵያ እየመከረች ነው!