ዓለም አቀፍ የልማት አጋሮች ልዑካን ቡድን በምክክሩ ቦታ ተገኝቶ ሂደቱን ተመለከተ
ነሀሴ 13/2018 ዓ.ም
በተባበሩት መንግስታት የልማት ድርጅት (UNDP) እና በኢፌዲሪ የገንዘብ ሚኒስቴር አስተባባሪነት ለኮሚሽኑ ድጋፎችን የሚያደርጉ የተለያዩ ሀገራት ወኪሎች ልዑካን ቡድን አባላት የሀገራዊ ምክክር ጉባኤውን አሁናዊ ሂደት ተዘዋውረው ተመልክተዋል፡፡
አባላቱ ከጉብኝታቸው ባሻገር የሀገራዊ ምክክር ጉባኤውን ዐበይት ክንውን የተመለከተ ገለፃ በኮሚሽኑ ኮሚሽነሮች ቀርቦላቸዋል፡፡





