የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን

ኮሚሽኑ የድሬዳዋ ከተማ መስተዳድር ተሳታፊዎች ልየታን በሠላምና በተሳካ አኳኋን አጠናቀቀ፡፡

356430804 256813380373432 4767745042192657120 n

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በድሬዳዋ ከተማ መስተዳድር በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ የሚሳተፉ ተወካዮችን ከየማህበረሰብ ክፍሉ እንዲለዩ አድርጓል፡፡ ከሰኔ 14 እስከ ሰኔ 17 ቀን 2015 ዓ.ም በድሬዳዋ ከተማ በተደረገው የተሳታፊዎች ልየታ መርሃ ግብር በከተማ መስተዳድሩ ከሚገኙ ወረዳዎች ከእያንዳንዳቸው የተውጣጡ 9 የማህበረሰብ ክፍሎች ሀምሳ ሀምሳ ሰዎችን መርጠው በሂደቱም በቁጥር 4500 የሚሆኑ ተሳታፊዎች ተካፋይ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡ በዚሁ ክንውን ተሳታፊዎች በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ የሚሳተፉ ተወካዮቻቸውን የመረጡ ሲሆን በሀገራዊ ምክክሩ ላይ እንዲንፀባረቅላቸው የሚፈልጓቸውን አጀንዳዎች በቡድን ውይይቶቻቸው አመላክተዋል፡፡

 

354567617 256813870373383 8125012322989112914 n

354262636 256814073706696 3901454535500454396 n