የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን

ኮሚሽኑ በሶማሌ ክልል ሲቲ ዞን በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ ተሳታፊ የሚሆኑ ተወካዮችን እያስመረጠ ነው፡፡

siti zone

ከየካቲት 16 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በሺኒሌ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው ይህ መርሐ-ግብር ለሶስት ቀናት የሚቆይ ሲሆን በአጠቃላይ 1100 የሚሆኑ ተሳታፊዎችን ያሳትፋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በመድረኩ ከአይሻ፣ ሀዳጋላ እና ሺኒሌ ወረዳዎች የተውጣጡ ተሳታፊዎች ተወካዮቻቸውን ለመምረጥ ተገኝተዋል፡፡ መርሐ-ግብሩ በተመሳሳይ ሁኔታ በቀጣዮቹም ሁለት ቀናት የተቀሩትን የዞኑን ወረዳዎች በማሳተፍ ይቀጥላል፡፡

ለመድረኩ ተሳታፊዎች ስለሀገራዊ ምክክር እና ተያያዥ ጉዳዮች ግንዛቤ እንዲጨብጡ ስለምክክር ፅንሰ ሀሳብ፣ ኮሚሽኑ እስካሁን ስላከናወናቸው ተግባራት፣ ስለሀገራዊ ምክክር ሂደቶች እና ተሳታፊዎች ተወካዮቻቸውን ሲመርጡ ሊከተሏቸው ስለሚገቡ ሂደቶች በባለሙያ ገለፃ ተደርጎላቸዋል፡፡

ተሳታፊዎቹ ለአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ይወክሉናል የሚሏቸውን ሁለት ሁለት ግለሰቦች ከአንድ ተጠባባቂ ጋር በየወረዳቸው እና በየማህበረሰብ ክፍሎቻቸው ይመርጣሉ፡፡