የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ተወካዮች ጋር ውይይት አድርጓል፡፡

diplomat photo,,,

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን መስከረም 30 ቀን 2016 ዓ.ም ከ60 በላይ ከሚሆኑ የዓለም አቀፍ ተቋማት እና ዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ተወካዮች ጋር በስካይ ላይት ሆቴል ውይይት አድርጓል፡፡ ለሁለተኛ ጊዜ በተዘጋጀው በዚህ የትብብር እና አጋርነት መድረክ ላይ ኮሚሽኑን ወክለው በመርሃ-ግብሩ ላይ የተገኙት ኮሚሽነሮች በኮሚሽኑ ስለተከናወኑ ተግባራት ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ ይህ ሁነት የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ኮሚሽኑ የሚያከናውናቸውን ተግባራት በመረዳት ለበለጠ […]

ህትመቶች

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ – አማርኛና እንግሊዝኛ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ – አፋን ኦሮሞ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ – ትግርኛ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ – ሶማሊኛ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ – አፋርኛ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ – ሲዳምኛ    

ኮሚሽኑ በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ የዲያስፖራ ማህበር አባላት ጋር ውይይት አድርጓል፡፡

402082389 336809442373825 1278949545368035262 n

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በኢትዮጵያ ውስጥ ከሚገኙ የዲያስፖራ ማህበር አባላት ጋር  ህዳር 8 ቀን 2016 ዓ. ም በሚሊኒየም አዳራሽ ውይይት አድርጓል፡፡ የውይይት መድረኩ በሀገር ውስጥ የሚኖሩ የዲያስፖራው ማህበረሰብ አባላት በሀገራዊ ምክክር ሂደት ውስጥ ሊኖራቸው ስለሚገባ ንቁ ተሳትፎ እና ሊያደርጉ ስለሚገባው ድጋፍ ግንዛቤን ለመፍጠር ታስቦ የተዘጋጀ ነው፡፡ መርሐ-ግብሩም በኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፈሰር መስፈን አርያአያ የመክፈቻ ንግግር […]

ኮሚሽኑ በቤኒሻንጉል ክልል የተሳታፊ ልየታ እያደረገ ይገኛል

391691396 317074394347330 4256364185604428127 n

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በቤንሻንጉል ክልል በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ ተሳታፊ የሚሆኑ ተወካዮችን ከጥቅምት 02 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ከየማህበረሰብ ክፍሉ እንዲመረጡ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ ሂደቱም በሁለት ዙር የሚከናወን ሲሆን በመጀመሪያው ዙር 13 የአሶሳ ዞን ወረዳዎች የሚካተቱበት መርሃ ግብር ይካሄዳል፡፡ ከጥቂት ቀናት በኋላም 14 ወረዳዎች የሚሳተፉበት ሁለተኛው መርሃ ግብር ይካሄዳል፡፡ በክልሉ በአጠቃላይ የ22 ወረዳዎችና የአምስት […]

ኮሚሽኑ በሶማሌ ክልል የተባባሪ አካላት ስልጠና መስጠት ጀምሯል

401433585 335736559147780 8972404782134505446 n

ኮሚሽኑ በሶማሌ ክልል ለሚገኙ ተባባሪ አካላቱ ሲሰጥ የነበረውን የመጀመሪያውን ዙር ስልጠና ህዳር 06 ቀን 2016 ዓ.ም አጠናቋል፡፡ በጅግጅጋ ከተማ ለሶስት ቀናት ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ከስድስት ዞኖች የተውጣጡ ተባባሪ አካላት ተሳታፊዎች ሆነውበታል፡፡ በስልጠናው ላይ ተባባሪ አካላቱ ባደረጓቸው የቡድን ውይይቶች ላይ የክልሉን ዓውድ መሰረት አድርገው ከየማህበረሰብ ክፍሉ ተሳታፊዎችን ስለሚለዩባቸው መንገዶች ውይይቶች አድርገዋል፡፡ በስልጠናው ላይ የተሳተፉ ተባባሪ አካላት […]

ኮሚሽኑ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በምዕራብ ኦሞ ዞን የተሳታፊ ልየታ እያደረገ ይገኛል፡፡

401235477 333141006074002 8548509446813908312 n

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል በምዕራብ ኦሞ ዞን በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ ተሳታፊ የሚሆኑ ተወካዮችን ከዛሬ ጥቅምት 30 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ከየማህበረሰብ ክፍሉ እንዲመረጡ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ በጀሙ ከተማ ውስጥ እየተካሄደ የሚገኘው የመጀመሪያው ዙር መርሃ-ግብር ለሶስት ተከታታይ ቀናት ይቀጥላል፡፡ በዞኑ በአጠቃላይ የ7 ወረዳዎችን እና የ3 ከተማ አስተዳድር የማህበረሰብ ክፍሎችን በማሳተፍ […]

ኮሚሽኑ አዲስ በተቋቋመው በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለሚገኙ ተባባሪ አካላቱ ጥቅምት 22 ቀን 2016ዓ.ም ጀምሮ በሆሳዕና ከተማ ስልጠና መስጠት ጀምሯል፡፡

401016875 332634969457939 816547885170058521 n

በክልሉ ከሚገኙ 55 የወረዳ አስተዳደሮች እና 27 ከተማ አስተዳደሮች ለተውጣጡ 574 ሰልጣኝ ተባባሪ አካላት እየተሰጠ የሚገኘው ይህ ስልጠና ተባባሪ አካላቱ በየወረዳቸው ከሚገኙ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች ተሳታፊዎችን በመለየት ሂደት ውስጥ ለኮሚሽኑ እገዛ እንዲያደርጉ አቅማቸውን ለማጎልበት ነው፡፡ በዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ አዳራሽ የሚሰጠው ይህ ስልጠና ለሶስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ነው፡፡ በዚሁ ቆይታ ሰልጣኝ ተባባሪ አካላቱ ስለ ምክክር መሰረታዊ ፅንሰ […]

ኮሚሽኑ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለሚገኙ ተባባሪ አካላቱ ሲሰጥ የነበረውን ስልጠና ዛሬ ጥቅምት 24 ቀን 2016 ዓ.ም አጠናቋል

398672628 328559586532144 1388509867297744658 n

ኮሚሽኑ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለሚገኙ ተባባሪ አካላቱ ሲሰጥ የነበረውን ስልጠና ዛሬ ጥቅምት 24 ቀን 2016 ዓ.ም አጠናቋል፡፡ በሆሳዕና ከተማ ለሶስት ቀናት የተለያዩ ስነ-ዘዴዎችን በመጠቀም ሲሰጥ የነበረው ይህ ስልጠና ተባባሪ አካላቱ በተሳታፊ ልየታ ሂደት እና አተገባበር ላይ ግንዛቤ እንዲኖራቸው አድርጓል፡፡ ከ7 ዞኖች እና 3 ልዩ ወረዳዎች ተውጣጥተው ስልጠናውን የወሰዱት ተባባሪ አካላት የተሳታፊዎች ልየታ ሂደት ተዓማኒና ገለልተኛ […]

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን  የተሳታፊ ልየታ እያደረገ ይገኛል፡፡

metekel

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ ተሳታፊ የሚሆኑ ተወካዮችን ጥቅምት 13 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ከየማህበረሰብ ክፍሉ እንዲመረጡ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ በግልገል በለስ ከተማ መምህራን ኮሌጅ አዳራሽ ውስጥ እየተካሄደ የሚገኘው ይህ መርሃ-ግብር ለሁለት ተከታታይ ቀናት ይቀጥላል፡፡ በዛሬው ዕለት እየተካሄደ በሚገኘው የተወካዮች መረጣ ከግልገል በለስ ከተማ አስተዳደር፣ ዳንጉር ወረዳ፣ […]