የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በዚህ ሳምንት ያከናወናቸውን ዐበይት ተግባራት

weekly

በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ የተመራ የኮሚሽኑ ልዑክ ከአማራ ክልል አመራሮች ጋር ተወያይቷል፡፡ ኮሚሽኑ በሌሎች ክልሎች ያከናወናቸውን ስራዎች በአማራ ክልልም ማስቀጠል በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ውይይት ያደረገው፡፡ በአማራ ክልል በኩል የክልሉ ርዕሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ እና ሌሎች ኃላፊዎች በውይይቱ የተሰታፉ ሲሆን  ርዕሰ መስተዳደሩ የምክክር ኮሚሽኑ በቀጣይ በክልሉ ለሚያከናውናቸው ተግባራት ውጤታማነት አስፈላጊውን ድጋፍ […]

ኮሚሽኑ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሲያካሂድ የቆየውን የተወካዮች መረጣ አጠናቀቀ፡፡

south et

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ ተሳታፊ የሚሆኑ ተወካዮችን ከየካቲት 19 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ከየማህበረሰብ ክፍሉ ሲያስመርጥ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ የክልሉ የተወካዮች መረጣ 12 ዞኖችን በማካተት ሲከናወን የቆየ ሲሆን 9,300 የሚሆኑ ተሳተፊዎችን የሂደቱ አካል አድርጓል፡፡ በዚሁ ክንውን ተሳታፊዎች በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ የሚወክሏቸውን ተወካዮቻቸውን ከመምረጣቸው ባሻገር በሀገራዊ ምክክሩ ዙሪያ ግንዛቤ […]

ኮሚሽኑ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ ተሳታፊ የሚሆኑ ተወካዮችን ከየማህበረሰብ ክፍሉ በማስመረጥ ላይ ይገኛል፡፡

kore zone

በኬሌ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው ይህ መርሐ-ግብር በዞኑ ከሚገኙ 2 ወረዳዎች እና 1 የከተማ አስተዳደር የተውጣጡ 300 የሚሆኑ ተሳታፊዎችን በማሳተፍ ላይ ይገኛል፡፡ ተሳታፊዎች ለአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ይወክሉናል የሚሏቸውን ሁለት ሁለት ተወካዮች ከአንድ ተጠባባቂ ጋር እንዲመርጡ ይደረጋል፡:

ኮሚሽኑ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ ተሳታፊ የሚሆኑ ተወካዮችን ከየማህበረሰብ ክፍሉ አስመረጠ፡፡

south omo

በቱርሚ ከተማ የተካሄደው ይህ መርሐ-ግብር ከስድስት ወረዳዎች እና አንድ የከተማ አስተዳደር የተውጣጡ 700 የሚሆኑ ተሳታፊዎችን በማሳተፍ ተከናውኗል፡፡ በሂደቱ ለተሳታፊዎቹ በሀገራዊ ምክክሩ ዙሪያ እንዲሁም በሂደቱ በተወካይ ተሳትፎ በሚያደርጉበት ሁኔታ ላይ ገለጻ ተደርጎላቸዋል፡፡

ኮሚሽኑ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቡርጂ ዞን በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ ተሳታፊ የሚሆኑ ተወካዮችን ከየማህበረሰብ ክፍሉ እያስመረጠ ይገኛል፡፡

burji zone

በሶያማ ከተማ በመካሄድ ላይ የሚገኘው ይህ መርሐ-ግብር ከአንድ ወረዳ እና አንድ የከተማ አስተዳደር የተውጣጡ 200 የሚሆኑ ተሳታፊዎችን በማሳተፍ ላይ ይገኛል፡፡ በሂደቱ ኮሚሽኑ ለተሳታፊዎች ስለሀገራዊ ምክክር እና ተያያዥ ጉዳዮች በባለሙያ ገላፃ የተደረገላቸው ሲሆን ከዚህ በመቀጠልም ተሳታፊዎች ለአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ይወክሉናል የሚሏቸውን ተወካዮች እንዲመርጡ ይደረጋል፡፡

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለአጀንዳ አሰባሰብ አሰራር ስርዓቱ የሚያግዙ ግብዓቶችን ከባለድርሻ አካላት ሰበሰበ፡፡

addis ababa 1.

ኮሚሽኑ በክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ለሚያካሂደው አጀንዳ የማሰብሰብ ተግባር ያዘጋጀውን ረቂቅ የአሰራር ስርዓት በሚመለከተታቸው ባለድርሻ አካላት አስተችቶ ግብዓቶችን ሰብስቧል፡፡ በአዲስ አበባ ሀይሌ ግራንድ ሆቴል በተዘጋጀው በዚህ መርሐ-ግብር ከመላው ኢትዮጵያ የተውጣጡ ከ250 በላይ የሚሆኑ ተሳታፊዎች ታድመዋል፡፡ ከኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ፣ ከኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ምክር ቤት፣ ከኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት እንዲሁም ከመንግስት እና ከሌሎች የሚመለከታቸው […]

“የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት የሀገራዊ ምክክሩ ወሳኝ ምዕራፍ ነው፡፡” ፕሮፌሰር መሥፍን አርአያ

addis ababa 2

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የአጀንዳ ማሰባሰብና የሀገራዊ ጉባኤ ተሳታፊዎች የግብአት ማሰባሰቢያ የውይይት መድረክ በአዲስ አበባ እያካሄደ ይገኛል፡፡ በውይይት መድረኩ ከተለያዩ ማኅበራት፣ ተቋማትና የማኅበረሰብ ክፍሎች የተወከሉ አካላት እየተሳተፉ ነው፡፡ መድረኩን በንግግር የከፈቱት የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መሥፍን አርአያ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት የሀገራዊ ምክክሩ ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ለውይይቱ ተሳታፊዎች አስገንዝበዋል፡፡ በመሆኑም ሁሉም ባለድርሻ አካላት በሂደቱ ላይ በንቃት […]

ኮሚሽኑ በሰሜን ሸዋ ዞን በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ ተሳታፊ የሚሆኑ ተወካዮችን ከየማህበረሰብ ክፍሉ አስመርጧል፡፡

north shewa

በአዳማ ከተማ በተካሄደው በዚህ መርሐ-ግብር በዞኑ የሚገኙ ከ1,500 በላይ ተሳታፊዎች ወረዳዎቻቸውን እና የማህበረሰብ ክፍሎቻቸውን በመወከል እንዲሳተፉ አስችሏል፡፡ በሂደቱ ኮሚሽኑ ለተሳታፊዎች ስለሀገራዊ ምክክር እና ተያያዥ ጉዳዮች በባለሙያ ገላፃ ካደረገላቸው በኋላ ተሳታፊዎች ለአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ይወክሉናል የሚሏቸውን ተወካዮች እንዲመርጡ አድርጓል፡፡

ኮሚሽኑ በሶማሌ ክልል ሊበን ዞን በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ ተሳታፊ የሚሆኑ ተወካዮችን ዛሬ ከየማህበረሰብ ክፍሉ ማስመረጥ ጀመረ፡፡

somali liben

በፊልቱ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው መርሐ-ግብር ከደቃ ሱፍቱ፣ ቀርሳ ዱላ እና ፊልቱ ወረዳዎች የተውጣጡ ተሰብሳቢዎችን እያሳተፈ ይገኛል፡፡ በሂደቱ ኮሚሽኑ ለተሳታፊዎች ስለሀገራዊ ምክክር እና ተያያዥ ጉዳዮች በባለሙያ ገላፃ ያደረገ ሲሆን ተሳታፊዎች ለአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ይወክሉናል የሚሏቸውን ተወካዮች በመምረጥ ላይ ይገኛሉ፡፡ የሊበን ዞን የተወካዮች መረጣ ቅዳሜ የካቲት 30 ቀን 2016 ዓ.ም ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ኮሚሽኑ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጋሞ እና ጎፋ ዞኖች በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ ተሳታፊ የሚሆኑ ተወካዮችን ከየማህበረሰብ ክፍሉ አስመረጠ፡፡

south et gamo

በአርባ ምንጭ እና ሳውላ ከተሞች በትይዩ በመካሄድ ላይ የሚገኘው የጋሞ እና ጎፋ ዞኖች የተወካዮች መረጣ ከየወረዳው የተወከሉ የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍል ተወካዮችን በማካተት እየተካሄደ ይገኛል፡፡ በአርባ ምንጭ ከተማ እየተከናወነ የሚገኘው የጋሞ ዞን የተወካዮች መረጣ ለአራት ቀናት የሚቆይ ሲሆን 1,800 የሚሆኑ ተሳታፊዎች 20 ወረዳዎችንና የከተማ አስተዳደሮችን በመወከል ተሳታፊ እንዲሆኑ ያደርጋል፤ መርሐ-ግብሩም የካቲት 29 ቀን 2016 ዓ.ም ይጠናቀቃል […]