በኦሮሚያ ክልል የወረዳ የማኅበረሰብ ክፍሎች አጀንዳ የማሰባሰብ ምክክር እየተካሄደ ነው።
8/4/2017 በኦሮሚያ ክልል አዳማ ከተማ ትናንት ጠዋት በይፋ በተከፈተው የምክክር መድረክ ከ356 የክልሉ ወረዳዎች የተወጣጡ ከ7000 በላይ የማኅበረሰብ ክፍል ወኪሎች የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር መርሐግብር ጀምረዋል። በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደቱ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት የማኅበረሰብ ክፍሎች ሴቶች፣ ወጣቶች፣ ዕድሮች፣ መምህራን፣ የመንግሥት ሠራተኞች፣ ራሳቸውን የማገልጹበት መተዳደሪያ ያላቸው፣ ተፈናቃዮች፣ በባህላቸውና በሙያቸው ምክንያት የተገለሉ፣ ነጋዴዎች እና የማኅበረሰብ መሪዎች ናቸው። ተሳታፊዎቹ በ4 […]
የኦሮሚያ ክልል የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍ በይፋ ተጀመረ።
ታህሳስ 7/2017 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በኦሮሚያ ክልል የሚያከናውነው የአጀንዳ ማሰባሰብ የምክክር ምዕራፍ የመክፈቻ ሥነሥርዓት ዛሬ ጠዋት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩንቨርሲቲ ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ ንግግር ያደረጉት የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መሥፍን አርአያ (ፕሮፌሰር) በኢትዮጵያ ያሉ የአለመግባባት ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት መመካከር አስፈላጊ ነው ብለዋል። ኮሚሽኑ እጅግ መሠረታዊ የአለመግባባት መንስኤዎችን በአጀንዳ መልክ በማሰባሰብ ስኬታማ ሥራዎችን እያከናወነ መሆኑንም […]
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በዚህ ሳምንት ያከናወናቸውን ዐበይት ተግባራት
በኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ የተመራ የኮሚሽኑ ልዑክ ከአማራ ክልል አመራሮች ጋር ተወያይቷል፡፡ ኮሚሽኑ በሌሎች ክልሎች ያከናወናቸውን ስራዎች በአማራ ክልልም ማስቀጠል በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ውይይት ያደረገው፡፡ በአማራ ክልል በኩል የክልሉ ርዕሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ እና ሌሎች ኃላፊዎች በውይይቱ የተሰታፉ ሲሆን ርዕሰ መስተዳደሩ የምክክር ኮሚሽኑ በቀጣይ በክልሉ ለሚያከናውናቸው ተግባራት ውጤታማነት አስፈላጊውን ድጋፍ […]
ኮሚሽኑ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሲያካሂድ የቆየውን የተወካዮች መረጣ አጠናቀቀ፡፡
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ ተሳታፊ የሚሆኑ ተወካዮችን ከየካቲት 19 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ከየማህበረሰብ ክፍሉ ሲያስመርጥ መቆየቱ ይታወሳል፡፡ የክልሉ የተወካዮች መረጣ 12 ዞኖችን በማካተት ሲከናወን የቆየ ሲሆን 9,300 የሚሆኑ ተሳተፊዎችን የሂደቱ አካል አድርጓል፡፡ በዚሁ ክንውን ተሳታፊዎች በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ የሚወክሏቸውን ተወካዮቻቸውን ከመምረጣቸው ባሻገር በሀገራዊ ምክክሩ ዙሪያ ግንዛቤ […]
ኮሚሽኑ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ ተሳታፊ የሚሆኑ ተወካዮችን ከየማህበረሰብ ክፍሉ በማስመረጥ ላይ ይገኛል፡፡
በኬሌ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው ይህ መርሐ-ግብር በዞኑ ከሚገኙ 2 ወረዳዎች እና 1 የከተማ አስተዳደር የተውጣጡ 300 የሚሆኑ ተሳታፊዎችን በማሳተፍ ላይ ይገኛል፡፡ ተሳታፊዎች ለአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ይወክሉናል የሚሏቸውን ሁለት ሁለት ተወካዮች ከአንድ ተጠባባቂ ጋር እንዲመርጡ ይደረጋል፡:
ኮሚሽኑ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ ተሳታፊ የሚሆኑ ተወካዮችን ከየማህበረሰብ ክፍሉ አስመረጠ፡፡
በቱርሚ ከተማ የተካሄደው ይህ መርሐ-ግብር ከስድስት ወረዳዎች እና አንድ የከተማ አስተዳደር የተውጣጡ 700 የሚሆኑ ተሳታፊዎችን በማሳተፍ ተከናውኗል፡፡ በሂደቱ ለተሳታፊዎቹ በሀገራዊ ምክክሩ ዙሪያ እንዲሁም በሂደቱ በተወካይ ተሳትፎ በሚያደርጉበት ሁኔታ ላይ ገለጻ ተደርጎላቸዋል፡፡
ኮሚሽኑ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ቡርጂ ዞን በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ ተሳታፊ የሚሆኑ ተወካዮችን ከየማህበረሰብ ክፍሉ እያስመረጠ ይገኛል፡፡
በሶያማ ከተማ በመካሄድ ላይ የሚገኘው ይህ መርሐ-ግብር ከአንድ ወረዳ እና አንድ የከተማ አስተዳደር የተውጣጡ 200 የሚሆኑ ተሳታፊዎችን በማሳተፍ ላይ ይገኛል፡፡ በሂደቱ ኮሚሽኑ ለተሳታፊዎች ስለሀገራዊ ምክክር እና ተያያዥ ጉዳዮች በባለሙያ ገላፃ የተደረገላቸው ሲሆን ከዚህ በመቀጠልም ተሳታፊዎች ለአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ይወክሉናል የሚሏቸውን ተወካዮች እንዲመርጡ ይደረጋል፡፡
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ለአጀንዳ አሰባሰብ አሰራር ስርዓቱ የሚያግዙ ግብዓቶችን ከባለድርሻ አካላት ሰበሰበ፡፡
ኮሚሽኑ በክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች ለሚያካሂደው አጀንዳ የማሰብሰብ ተግባር ያዘጋጀውን ረቂቅ የአሰራር ስርዓት በሚመለከተታቸው ባለድርሻ አካላት አስተችቶ ግብዓቶችን ሰብስቧል፡፡ በአዲስ አበባ ሀይሌ ግራንድ ሆቴል በተዘጋጀው በዚህ መርሐ-ግብር ከመላው ኢትዮጵያ የተውጣጡ ከ250 በላይ የሚሆኑ ተሳታፊዎች ታድመዋል፡፡ ከኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ፣ ከኢትዮጵያ ሲቪል ማህበራት ምክር ቤት፣ ከኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት እንዲሁም ከመንግስት እና ከሌሎች የሚመለከታቸው […]
“የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት የሀገራዊ ምክክሩ ወሳኝ ምዕራፍ ነው፡፡” ፕሮፌሰር መሥፍን አርአያ
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የአጀንዳ ማሰባሰብና የሀገራዊ ጉባኤ ተሳታፊዎች የግብአት ማሰባሰቢያ የውይይት መድረክ በአዲስ አበባ እያካሄደ ይገኛል፡፡ በውይይት መድረኩ ከተለያዩ ማኅበራት፣ ተቋማትና የማኅበረሰብ ክፍሎች የተወከሉ አካላት እየተሳተፉ ነው፡፡ መድረኩን በንግግር የከፈቱት የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መሥፍን አርአያ የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት የሀገራዊ ምክክሩ ወሳኝ ምዕራፍ መሆኑን ለውይይቱ ተሳታፊዎች አስገንዝበዋል፡፡ በመሆኑም ሁሉም ባለድርሻ አካላት በሂደቱ ላይ በንቃት […]
ኮሚሽኑ በሰሜን ሸዋ ዞን በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ ተሳታፊ የሚሆኑ ተወካዮችን ከየማህበረሰብ ክፍሉ አስመርጧል፡፡
በአዳማ ከተማ በተካሄደው በዚህ መርሐ-ግብር በዞኑ የሚገኙ ከ1,500 በላይ ተሳታፊዎች ወረዳዎቻቸውን እና የማህበረሰብ ክፍሎቻቸውን በመወከል እንዲሳተፉ አስችሏል፡፡ በሂደቱ ኮሚሽኑ ለተሳታፊዎች ስለሀገራዊ ምክክር እና ተያያዥ ጉዳዮች በባለሙያ ገላፃ ካደረገላቸው በኋላ ተሳታፊዎች ለአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ይወክሉናል የሚሏቸውን ተወካዮች እንዲመርጡ አድርጓል፡፡