የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን

ኮሚሽኑ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለሚገኙ ተባባሪ አካላቱ ሲሰጥ የነበረውን ስልጠና ዛሬ ጥቅምት 24 ቀን 2016 ዓ.ም አጠናቋል

398672628 328559586532144 1388509867297744658 n

ኮሚሽኑ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ለሚገኙ ተባባሪ አካላቱ ሲሰጥ የነበረውን ስልጠና ዛሬ ጥቅምት 24 ቀን 2016 ዓ.ም አጠናቋል፡፡ በሆሳዕና ከተማ ለሶስት ቀናት የተለያዩ ስነ-ዘዴዎችን በመጠቀም ሲሰጥ የነበረው ይህ ስልጠና ተባባሪ አካላቱ በተሳታፊ ልየታ ሂደት እና አተገባበር ላይ ግንዛቤ እንዲኖራቸው አድርጓል፡፡

ከ7 ዞኖች እና 3 ልዩ ወረዳዎች ተውጣጥተው ስልጠናውን የወሰዱት ተባባሪ አካላት የተሳታፊዎች ልየታ ሂደት ተዓማኒና ገለልተኛ እንዲሆን ለማረጋገጥ ከኮሚሽኑ ጋር በጋራ እንደሚሰሩ ይጠበቃል::

በመቀጠልም በስልጠናው ላይ የተሳተፉ ተባባሪ አካላት ወደየወረዳዎቻቸው በመሄድ በኮሚሽኑ ከተለዩት የማህበረሰብ

ክፍሎች ተሳታፊዎችን በመለየት ረገድ የሂደቱን ተዓማኒነት በተመለከተ እገዛ ያደርጋሉ፡፡

398732189 329609753093794 4819089177363057898 n