የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን

ባለድርሻ አካላት አጀንዳዎቻቸውን ለይተው አጠናቀቁ፡፡

አዲስ 3

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአዲስ አበባ ከተማ እያካሄደ የሚገኘው የአዲስ አበባ ከተማ የምክክር ምዕራፍ ለስድስተኛ ቀን ዛሬም ቀጥሎ ውሏል፡፡ አምስቱ የምክክር ባለድርሻ አካላት ትላንት እና ዛሬ ከሰዓት በፊት በነበረው መርሃ-ግብር የአጀንዳ ሀሳቦቻቸውን በቡድን ሆነው ሲያጠናቅሩና ሲያደራጁ ቆይተዋል፡፡ ባለድርሻ አካላቱ ያጠናቀሯቸውን እና ያደራጇቸውን አጀንዳዎች በቃለ-ጉባኤ በማዘጋጀት ለአጠቃላይ መድረኩ የሚያቀርቡላቸውን ተወካይ ግለሰቦችንም መርጠዋል፡፡ ዛሬ ከሰአት በተካሄደው መርሃ-ግብር […]