የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከኢትዮጵያ የፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ጋር ውይይት አካሄደ፡፡

365471930 279285424792894 4377453634882040428 n

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ጋር ሐምሌ 28 ቀን 2015 ዓ.ም በካፒታል ሆቴል ውይይት አድርጓል፡፡ በኮሚሽኑ አዘጋጅነት የተደረገው የዚህ ውይይት ዓላማ ኮሚሽኑ በጋራ ምክር ቤቱ አጋዥነት በሰራቸው ስራዎች ላይ ገለፃ ለመስጠት እና በቀጣይም በሚሰራቸው ስራዎች ላይ ውይይቶችን ለማድረግ ነው፡፡ ኮሚሽኑ በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት የሚሳተፉ ተወካዮችን ከየማህበረሰብ ክፍሉ ሲያስመርጥ የሂደቱን ግለፀኝነትና እና ተዓማኒነት በማረጋገጥ ረገድ ለኮሚሽኑ እገዛን ሲያደርጉ ከነበሩ ተባባሪ አካላት መካከል የኢትዮጵያ የፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አንዱ እነደሆነ የሚታወስ ነው፡፡

በውይይት መድረኩ ላይ ኮሚሽኑ ተሳታፊዎችን ለመለየት በተንቀሳቀሰባቸው የተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች የፖሊቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤቱ ለኮሚሽኑ ትልቅ እገዛን እንዳደረገ ተገልጿል፡፡ በተጨማሪም በውይይቱ ላይ ከተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄዎች እና ገንቢ ሀሳቦች የቀረቡ ሲሆን ኮሚሽኑ በተሳታፊዎች ልየታ ሂደት እና ሌሎች ጉዳዮች ላይ ሊያስተካክላቸው ስለሚገባቸው ነገሮች ሀሳቦችና እና አስተያየቶች ቀርበዋል፡፡

የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርአያ በውይይቱ ላይ እንደጠቀሱት ሁሉም በትጥቅ ትግል ወይም በሰላማዊ መንገድ ተሰልፈው ያሉ የፖለቲካ ሀይሎች የሀገራዊ ምክክሩ አካል እንዲሆኑ ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እያለ ኮሚሽኑ ከዚህ ቀደም ባቀረባቸው መሰል ጥሪዎች ምላሽ በመስጠት በዝግጅቱ ላይ የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃ አውጪ ግንባር (ኦብነግ) ተወካዮች ፓርቲውን ወክለው የተገኙ ሲሆን ከኮሚሽኑ ጋር በጋራ ለመስራት ያላቸውን ፈቃደኝነትም ገልጸዋል፡፡

365468468 279285718126198 1249440334945139681 n

365559230 279285521459551 2553480000169741399 n

365579143 279285494792887 6894302019531418771 n

365654969 279285474792889 1905893209060445317 n