የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን

ኮሚሽኑ የሐረሪ ክልል የተሳታፊዎች ልየታን በተሳካ ሁኔታ አከናወነ፡፡

354459126 251858394202264 1236656366855401079 n

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሐረሪ ክልል በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት ላይ የሚሳተፉ ተወካዮችን ከየማህበረሰብ ክፍሉ እንዲለዩ አድርጓል፡፡ በሐረር ከተማ ከሰኔ 5 እስከ ሰኔ 7 ቀን 2015 ዓ.ም በተደረገው የተሳታፊዎች ልየታ መርሃ ግብር በክልሉ ከሚገኙ 9 ወረዳዎች የተውጣጡ 9 የማህበረሰብ ክፍሎች እያንዳንዳቸው 50 ሰዎችን መርጠው በሂደቱም ከ 4,000 በላይ ተሳታፊዎች ተካፋይ ሆነዋል፡፡ በዚህም መሰረት በክልሉ በተደረገው የተሳታፊዎች ልየታ 324 ተወካዮች በቀጣይ ለሚደረገው የአጀንዳ ማሰባሰብ ስራ እንዲወከሉ በክልሉ ከሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎች ተመርጠዋል፡፡

በሌላ በኩልም ተሳታፊዎች በቡድን ባደረጓቸው ውይይቶች በሀገራዊ ምክክሩ ላይ እንዲነሱ የሚፈልጓቸውን አጀንዳዎች ያመላከቱ ሲሆን በተወካዮቻቸውም አማካኝነት በክልል በሚደረገው የአጀንዳ ማሰባሰብ ስራ ያመላከቱዋቸው አጀንዳዎች እንደሚንፀባረቁላቸው ይጠበቃል፡፡

 

354042659 251858340868936 4117462820242977748 n

354589517 251858244202279 585868294211361416 n