የሃሳብ ልዩነቶችን ከማስተናገድ ያለፈ ሀገራዊ ምክክር

የሃሳብ ልዩነቶችን ከማስተናገድ ያለፈ ሀገራዊ ምክክር ህዳር 29/2018 ዓ.ም የሃሳብ ብዝሃነት በሚስተዋልባቸው የዓማችን የተለያዩ ሕብረተሰቦች ምክክር እንደ መጀመሪያ አማራጭ ተደርጎ ሲወሰድ እምብዛም አይስተዋልም፡፡ በአንፃሩ ደግሞ ተሞክሮዎች አንደሚያሳዩት የሃሳብ ልዩነቶች ላይ ግልፅ፣ አካታች እና ተዓማኒነት ባላቸው መልኩ ውይይት ከተደረገባቸው የሀገርን ቁስል እና ሕመም የመሻር አቅማቸው ከፍተኛ መሆኑ ነው፡፡ ሀገራዊ ምክክርም ‘’ዜጎች ሲደማመጡ መተማመንን ያድሳሉ፤ ዜጎች ሲነጋገሩ […]
ኢዜማ አጀንዳዎቹን ለኮሚሽኑ አስረከበ

“የፖለቲካ ፓርቲዎች ለሀገራዊ ምክክሩ ስኬት እያደረጉ ያሉትን አስተዋጽኦ አጠናክረው ሊቀጥሉ ይገባል” ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መሥፍን አርአያ ህዳር 26/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ ፓርቲ (ኢዜማ) የሀገራዊ ምክክር አጀንዳዎቹን ለኮሚሽኑ አስረክቧል። አጀንዳዎቹን የፓርቲው መሪ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እና ሌሎች አመራሮች ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነሮች አስረክበዋል። በርክክብ ሥነሥርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መሥፍን አርአያ፤ […]
የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በኢትዮጵያ ከሚገኙ የሙያ ማህበራት ጋር ውይይት አካሄደ

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በኢትዮጵያ ከሚገኙ የሙያ ማህበራት ጋር ውይይት አካሄደ ህዳር 25/2018 ዓ.ም ኮሚሽኑ ”የኢትዮጵያ የሙያ ማህበራት የላቀ ተሳትፎ ለሀገራዊ ምክክር ውጤታማነት“በሚል መሪ ሀሳብ በኢትዮጵያ ከሚገኙ የሙያ ማህበራት ጋር የምክክር መድረክ ዛሬ ህዳር 25/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ኢንተር ሌግዠሪ ሆቴል አካሂዷል። በምክክር መድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ (ፕሮፌሰር) ለሀገራዊ ምክክር […]
ለሀገራዊ ምክክሩ ሂደት መሳካት የሃይማኖት ተቋማትና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሚና ከፍተኛ ነው- ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕሮፌሰር)

ለሀገራዊ ምክክሩ ሂደት መሳካት የሃይማኖት ተቋማትና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ሚና ከፍተኛ ነው- ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕሮፌሰር) ህዳር 23/2081 ዓ.ም (አዲስ አበባ) የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የኢትዮጵያ የሐይማኖት ተቋማትና የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የላቀ ተሳትፎ ለሀገራዊ ምክክር ውጤታማነት በሚል መሪ ሀሳብ የምክክር መድረክ ዛሬ ህዳር 23/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ካፕታል ሆቴል አካሂዷል። በምክክር መድረኩ ንግግር ያደረጉት […]
ኮሚሽኑ ከሴቶች፣ወጣቶችና አካል ጉዳተኞች ጋር ተወያየ

ኮሚሽኑ ከሴቶች፣ወጣቶችና አካል ጉዳተኞች ጋር ተወያየ ህዳር 14/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በኦሮሚያና አፋር ክልሎች ከሚገኙ ሴቶች፣ወጣቶችና አካል ጉዳተኞች ጋር ተወያይቷል። ውይይቱ በኦሮሚያ ክልል በአዳማና ጅማ ከተሞች በሁለት ክላስተር እየተካሄደ ሲሆን በአፋር ክልል ደግሞ በሰመራ ከተማ ተካሂዷል። የኢትዮጵያን ችግሮች ከአፈሙዝ ይልቅ በውይይቱ የመፍታት ባህል እንዲሰርፅ ለማድረግ የወጣቶች፣ የሴቶችና የአካል ጉዳተኞች ተሳትፎ አስፈላጊ ነው። በሶስቱም […]
“ለቀሪ የሀገራዊ ምክክር ሂደቶች መሳካት የፖለቲካ ፓርቲዎች ንቁ ተሳትፎ አስፈላጊ ነው” – ዋና ኮሚሽነር መሥፍን አርአያ(ፕሮፌሰር)

“ለቀሪ የሀገራዊ ምክክር ሂደቶች መሳካት የፖለቲካ ፓርቲዎች ንቁ ተሳትፎ አስፈላጊ ነው” – ዋና ኮሚሽነር መሥፍን አርአያ(ፕሮፌሰር) ህዳር 8/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን “የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የላቀ ተሳትፎ ለሀገራዊ ምክክር ውጤታማነት” በሚል መሪ ሃሳብ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በአዳማ ከተማ ከህዳር 5-6/2018 ዓ.ም ተወያይቷል፡፡ ዋና ኮሚሽነር መሥፍን አርአያ (ፕሮፌሰር) በዚህ መድረክ ባስተላለፉት መልዕክት ኮሚሽኑ ወደ ሀገራዊ […]
የሀገራዊ ምክክር ሕግን እና ሕጋዊ ስርዓትን አደጋ ላይ የሚጥል ነውን?

የሀገራዊ ምክክር ሕግን እና ሕጋዊ ስርዓትን አደጋ ላይ የሚጥል ነውን? ህዳር 1/2018 ዓ.ም በተለያዩ አጋጣሚዎች ሲገለፅ እንደቆየው የሀገራዊ ምክክር የዲሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ሂደት ነው፡፡ ይህ በእንዲህ እያለ ሂደቱ ራሱን በቻለ ህጋዊ ማዕቀፍ የሚተዳደር ሲሆን የሂደቱ ውጤቶች ህጋዊ ስርዓትን አደጋ ላይ ሊጥሉ እንደሚችሉ ግንዛቤ ያላቸው አካላት ይስተዋላሉ፡፡ በእርግጥ የሀገራዊ ምክክር ሂደቶች ከህግ ፍልስፍናዎች እና መሰረታዊ አስተምህሮቶች […]
“ኮሚሽኑ ለሚያከናውነው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ሙያዊ ሥልጠናዎች ጠቃሚ ናቸ” ኮሚሽነር መላኩ ወልደማርያም

“ኮሚሽኑ ለሚያከናውነው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ሙያዊ ሥልጠናዎች ጠቃሚ ናቸ” ኮሚሽነር መላኩ ወልደማርያም ጥቅምት 24/2018 ዓ.ም ቤርጎፍ ፋውንዴሽን ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም ጋር በመተባበር ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ኮሚሽን አማካሪ ኮሚቴ ሥልጠና እየሰጠ ነው። በሥልጠናው መጀመሪያ ላይ ተገኝተው የእንኳን ደኅና መጣችሁ መልዕክት ያስተላለፉት ኮሚሽነር መላኩ ወልደማርያም፤ ሥልጠናው ለኮሚሽኑ ስልታዊ ግቦች እንደሚያግዝ ተናግረዋል። ሥልጠናውን ያዘጋጁ አጋር አካላትን ያመሰገኑት […]
ሀገራዊ ምክክር መቼ ሊካሄድ ያችላል?

ሀገራዊ ምክክር መቼ ሊካሄድ ያችላል? ጥቅምት 24/2018 ዓ.ም በዓለማችን የሚገኙ የተለያዩ ሀገራት ሀገራዊ ምክክርን ለማካሄድ ሲወጥኑ የተለያዩ ውስጣዊ ችግሮቻቸውን ለመፍታት እንደሆነ እሙን ነው፡፡ ሂደቱ ላለመግባባት መንስኤ የሆኑ ጉዳዮችን በመለየት ባለድርሻ አካላት ምክክር እንዲያደርጉ በመጋበዝ ሀገራዊ መግባባት እና ሰላም እንዲሰፍን አበክሮ ይሰራል፡፡ ይህ በእንዲህ እያለ ሀገራዊ ምክክርን ለማካሄድ አመቺ ጊዜ እና ዓውድ መፈጠር እንዳለበት ተሞክሮዎች ያመለክታሉ፡፡ […]
የሌሎች ሀገራት የሀገራዊ ምክክር ሂደቶች ለሀገራችን ኢትዮጵያ ምን ትምህርት ይሰጣሉ?

የሌሎች ሀገራት የሀገራዊ ምክክር ሂደቶች ለሀገራችን ኢትዮጵያ ምን ትምህርት ይሰጣሉ? ጥቅምት 17/2018 ዓ.ም በተለያዩ ሀገራት የተከናወኑ የሀገራዊ ምክክር ሂደቶች ለሀገራችን በጎ የሚሆን ትምህርትን አስቀምጠውልን እንዳለፉ የስነ-ምክክር መዛግብት ያስረዳሉ፡፡ የደቡብ አሜሪካዊቷ ኮሎምቢያ እ.አ.አ ከ2012-2016 ባካሄደችው የሀገራዊ ምክክር ሂደት በርካታ ተሞክሮዎች እንደተገኙበት ይነገራል፡፡ ሂደቱም በዋነኝነት የግጭት እና የሀሳብ ልዩነቶች መንስኤ የሆኑትን ጉዳዮች ከስር መሰረታቸው በመለየቱ ረገድ አመርቂ […]