የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን

ኮሚሽኑ በምክክሩ ለሚሳተፉ ባለድርሻ አካላት ገለፃ አደረገ፡፡

አዲስ 7

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአዲስ አበባ ከተማ በምክክር ምዕራፍ ላይ ተሳታፊ ለሚሆኑ ባለድርሻ አካላት ገለፃ አድርጓል፡፡ ከግንቦት 21 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ የምክክር ምዕራፍን በይፋ ያስጀመረው ኮሚሽኑ ዛሬ ግንቦት 23 ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ለተውጣጡ ወኪሎች በአደዋ ሙዚየም አዳራሽ ስለ ምክክር ምዕራፉ ገለፃ እና ማብራሪያ ሰጥቷል፡፡ በዕለቱ በተዘጋጀው የገለፃ መርሃ-ግብር የፓለቲካ ፓርቲ ተወካዮች፣ […]

የሕብረተሰብ ተወካዮች አጀንዳቸውን ለይተው ለኮሚሽኑ አስረከቡ፡፡

አዲስ 6

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በአዲስ አበባ ከተማ ከግንቦት 21 ጀምሮ ላለፉት ሶስት ተከታታይ ቀናት ሲያስተባብር የነበረውን ክንውን ጨርሷል፡፡ በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ወኪሎች በአጀንዳ ሀሳቦች ላይ ሲያደርጉት የነበረው ውይይት እና ልየታ ዛሬ መቋጫውን አግኝቷል፡፡ የከተማዋን ነዋሪ በተለያዩ ቡድኖች ወክለው የተገኙ ከ2000 በላይ ተወካዮች ከወከላቸው የሕብረተሰብ ክፍል በአደራ በተቀበሏቸው የአጀንዳ ሀሳቦች ላይ ላለፉት ሶስት […]

ኮሚሽኑ እያከናወነ በሚገኘው የምክክር ምዕራፍ ምን ዓይነት ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ?

አዲስ 9

• ግንቦት 21 ቀን 2016 ዓ.ም ከ2000 በላይ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን በመወከል የሚሳተፉ ተሳታፊዎች በአድዋ ሙዚየም አዳራሽ ተገኝተው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የምክክር ምዕራፍ ጀምረዋል፡፡ • ከግንቦት 21/2016 ዓ.ም ግማሽ ቀን በኋላ ተሳታፊዎች በየሕብረተሰብ ክፍሎቻቸው በመሆን ከየማህበረሰብ ክፍሎቻቸው በአደራ ያመጧቸው የአጀንዳ ሀሳቦች ላይ ውይይት በማድረግ ላይ ናቸው፡፡ • ዛሬ ግንቦት 22 ቀን 2016 ዓ.ም በየህብረተሰብ […]

“ሀገራዊ ችግሮችን ከሥረ መሠረታቸው ለመፍታት ሴቶች ያላቸው ክህሎት የላቀ ነው!” ፕሬዝዳንት ሳሕለወርቅ ዘውዴ

blank 4 grids collage

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን “በሀገራዊ ምክክሩ የሴቶች ተሳትፎና ሚና” በሚል መሪ ሃሳብ የውይይት መድረክ አካሄደ፡፡ በመድረኩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሳሕለወርቅ ዘውዴ፤ ሀገራዊ ምክክር በአካታችነት መርህ የሚመራ መኾኑን ማረጋገጥ ለዘላቂ ሰላም ጠቃሚ ነው ብለዋል። በኢትዮጵያ ግጭቶችና ሥር የሰደዱ ችግሮችን ለመፍታት ከሀገራዊ ምክክር ሌላ መፍትሔ እንደሌለም ገልጸዋል። ሴቶች በሀገራዊ ምክክር ሂደቱ የሚሳተፉት መብታቸው ስለኾነ […]

የኮሚሽኑ የአማካሪ ኮሚቴ ለኮሚሽኑ ምክር ቤት የምክረ ሀሳብ ሰነድ አቀረበ፡፡

collage (1)

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የአማካሪ ኮሚቴ በ13 አበይት ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ምክረ-ሀሳቦችን ያካተተ ሰነድ ዛሬ በኮሚሽኑ ፅ/ቤት አቅርቦ ውይይት አድርጓል፡፡ የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርአያ (ፕ/ር) በውይይቱ ላይ ባደረጉት ንግግር የአማካሪ ኮሚቴው በተለያዩ ጉዳዮች ላይ የሚያቀርባቸው ምክረ-ሀሳቦች የኮሚሽኑን ስራዎች ለማሻሻል ትልቅ ሚናን እንደሚጫወቱ ገልፀዋል፡፡ የኮሚሽኑ የአማካሪ ኮሚቴ በሙያቸው፣ በትምህርት ዝግጅታቸው፣ በህዝብ ዘንድ ባላቸው ቅቡልነት እንዲሁም […]

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ኮሚሽነሮች ከብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ከፍተኛ አመራሮች ጋር ተወያዩ።

438745430 426737850047650 3764992894542447321 n

ዋና ኮሚሽነር መስፍን አርዓያ (ፕ/ር) ከሌሎች ኮሚሽነሮች ጋር በጋራ አዲስ በተሾሙት የብሔራዊ ተሃድሶ ኮሚሽን ኮሚሽነር ተመስገን ጥላሁን የተመራውን የኮሚሽኑን ከፍተኛ የስራ ኋላፊዎች ልዑክ በፅ/ቤታቸው ተቀብለው ውይይት አድርገዋል። ሚያዚያ 14/2016 ዓ.ም የተካሄደው ይህ የውይይት መድረክ ሁለቱ ኮሚሽኖች በሚያከናውኗቸው ሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ የሀሳብ ልውውጥ ተደርጎበታል፡

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የስራ አመራሮችና ባለሙያዎች በቀሪ አስር ወራት የኮሚሽኑን ስራ የሚያቀላጥፉበት አቅጣጫ ተሰጠ፡፡

440069329 426015293453239 5786150789023894699 n

ኮሚሽኑ ከዪኤንዲፒ ጋር ተባብሮ በውጤት ተኮር ሥራ አመራር፣ በተቋማዊ ባህል፣ በዕቅድ መንደፍና አተገባበር እንዲሁም በውጤት ምዘና ዙሪያ ለተቋሙ የስራ አመራሮችና ባለሙያዎች ስልጠና እየሰጠ ይገኛል። ለአመራሮቹ እና ባለሙያዎቹ አቅጣጫ የተሰጠበትን ስልጠና የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ተገኘወርቅ ጌጡ (ዶ/ር) እና ኮሚሽነር ብሌን ገ/መድህን ተገኝተው ሰጥተዋል። ኮሚሽነሮቹ ስራ አመራሮችና ባለሙያዎች በተቀናጀ ሁኔታ በቀሪ አስር ወራት የኮሚሽኑን ስራ እንዴት ማቀላጠፍ እንዳለባቸው […]

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በኦሮሚያ ክልል በሚገኙ 348 ወረዳዎችና ከተማ አስተዳደሮች ሲያካሂድ የነበረውን የተሳታፊዎች ልየታ ስራ ማጠናቀቁን አስታወቀ፡፡

mergedimages

ኮሚሽኑ በኦሮሚያ ክልል በአዳማ፣ በሀረር፣ በጅማ እና በሻሸመኔ ክላሰተር ሲያካሂድ የነበረውን በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት የሚሳተፉ ተወካዮችን የማስመረጥ ሂደት ማጠናቀቁን በማስመልከት የመዝጊያ መርሀ-ግብር በሻሸመኔ ከተማ አካሂዷል፡፡ በዚህ የመዝጊያ መርሀ-ግብር የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕ/ር መስፍን ዓርዓያ፣ ም/ዋና ኮሚሽነር ሂሩት ገ/ስላሴ እና ኮሚሽነር ተገኘወርቅ ጌጡ ( ዶ/ር) ተገኝተዋል:: የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ዋና ኮሚሽነር ፕ/ር መስፍን ዓርዓያ ባደረጉት ንግግር […]

ከምስራቅ ጉጂ ዞን 11 ወረዳዎች የመጡ የህብረተሰብ ክፍሎች በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት የሚሳተፉ ወኪሎቻቸውን መረጡ::

436300216 423265033728265 3717769399222700432 n

በኦሮሚያ ክልል በሻሸመኔ ከተማ እየተካሄደ ያለው የሻሸመኔ ክላስተር በአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት የሚሳተፉ ተወካዮችን የማስመረጥ ሂደት ዛሬ ሶስተኛ ቀኑን ይዟል፡፡ በሻሸመኔ ክላስተር ስር በሚገኙ ስድስት ዞኖች እየተከናወነ በሚገኘው የተወካዮች ምርጫ ሂደት ዛሬ ሚያዚያ 08/2016 ዓ.ም ከምስራቅ ጉጂ ዞን 11 ወረዳዎች የመጡ ህብረተሰብ ክፍሎች ተወካዮቻቸውን መርጠዋል፡፡ በምስራቅ ጉጂ ዞን ውስጥ የሚገኙ 11 ወረዳዎች፡- ዋደራ፣ ዳማ፣ አናሶራ፣ አረዳ […]

ጃፓን ኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ ለምትሰራው ስራ ድጋፏን አጠናክራ እንደምትቀጥል በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ገለፁ፡፡

436384331 422547580466677 7408357033304379797 n

የጃፓን መንግሥት ከተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም (UNDP) ጋር በመተባበር ለኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን 12 ተሸከርካሪዎችን በዛሬው ዕለት አስረክቧል፡፡ በኢትዮጵያ የጃፓን አምባሳደር ሺባታ ሂሮኖሪ ልገሳው የጃፓን መንግሥት ለሀገራዊ ምክክሩ መሳካት ያለውን ድጋፍ የሚያሳይ ነው ብለዋል፡፡ ኮሚሽኑ ለሚያከናውናቸው ተግባራት ቅልጥፍና ልገሳው ጉልህ አስተዋፅኦ እንደሚኖረውም አክለዋል፡፡ ኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ ለምትሰራው ስራ የጃፓን መንግሥት ወደፊትም ድጋፉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል […]