የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን

ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤው የተለዩ አጀንዳዎች በምን መስፈርት ተመረጡ?

ለሀገራዊ ምክክር ጉባኤው የተለዩ አጀንዳዎች በምን መስፈርት ተመረጡ? በኮሚሽነር አምባዬ ኦጋቶ (ዶ/ር)

ግንቦት 14/2018 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አጀንዳዎችን ለሃይማኖት ተቋማትና ለሲቪክ ማኅበራት አቅርቦ ግብዓት አሰባስቧል።

ዛሬ ግንቦት 14/2018 ዓ.ም በተካሄደው መድረክ ላይ የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ አጀንዳዎች የተቀረፁበትን መሥፈርት የኮሚሽኑ ኮሚሽነር አምባዬ ኦጋቶ (ዶ/ር) አቅርበዋል።

እንደ ኮሚሽነር አምባዬ ማብራሪያ መስፈርቶቹ የሚከተሉት ናቸው

👉 የጉዳዩ ጭብጥ የህገመንግስት ማሻሻልን የሚያስከትል ከሆነ

👉ጉዳዩ በሀገሪቱ ያሉ ለዘመናት ሲንከባለሉ የመጡ የአለመግባባት መንስኤዎችን እና ችግሮችን በትክልል የሚዳስስ እና በጉዳዩ ላይ መመካከር ችግሩን በትክክል የሚፈታ ሆኖ ሲገኝ፡፡

👉ጉዳዩ ላይ ምክክር ቢደረግበት በህዝብ እና በሕዝብ መካከል ያሉትን ግንኙነቶች በማሻሻል መተማመንን የሚፈጥር ሆኖ ሲገኝ፡፡

👉አዲስ የፖለቲካ ስርዓት ለመፍጠር የሚረዳ ጉዳይ ሆኖ ሲገኝ

👉ጉዳዩ ላይ ምክክር ቢደረግበት በህዝብ እና በመንግስት መካከል ያሉትን ግንኙነቶች በማሻሻል መተማመንን የሚፈጥር ሆኖ ሲገኝ፡፡

👉የዲሞክራሲ ስርዓት እንዲገነባ ለማስቻል አስተዋጽኦ የሚያደርግ ሲሆን፡፡

👉ቅቡልነት ያለው ሀገረ-መንግስት በመገንባት ሂደት ጠንካራ መሰረት ለመጣል የሚያግዝ ሆኖ ሲገኝ፡፡

👉የሰላም ግንባታ፡- ወቅታዊ ችግሮችን ዘላቂ በሆነ መንገድ በመፍታት አስተማማኝ ሰላም ለመፍጠር የሚያግዝ ሆኖ ሲገኝ፡፡

👉ለሀገራዊ መግባባት አስተዋጽ የሚያደርግ ሲሆን፡፡

👉የተሸረሸሩ ሀገራዊ እሴቶችን ለማደስ አስተዋጽዖ የሚያደርግ ሲሆን፡፡

ኢትዮጵያ እየመከረች ነው!